“ምርጫው በሰላም እና በሥርዓት እየተካሄደ ነው” ኡሁሩ ኬንያታ
ባሕር ዳር: ግንቦት 24/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ልዑክ መሪና የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላማዊ ሁኔታ መጀመሩን ገልጸዋል።
ድምፅ መስጠት ዜጎች የሚወክሏቸውን መሪዎች በነፃነት የሚመርጡበት ትልቅ...
“ነፃ ኾነን በካርዳችን የምንፈልገውን መርጠናል” የደብረ ማርቆስ ከተማ ነዋሪዎች
ደብረማርቆስ፡ግንቦት 24/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የደብረ ማርቆስ ከተማ ነዋሪዎች 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ እያካሄዱ ይገኛሉ።
በከተማዋ በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች መራጮች ድምፃቸውን እየሰጡ ነው።
አሚኮ ያነጋገራቸው የከተማዋ ነዋሪዎች ነፃ ኾነው ለሚፈልጉት ድምፃቸውን ስለመስጠታቸው ተናግረዋል።
ምርጫ የአንድን ሀገር መፃኢ ዕድል የሚወስን...
የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲወስ (ዶ.ር) በምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምጽ ሰጡ።
አዲስ አበባ፡ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲወስ (ዶ.ር) በአዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ አራት ጥበበ ዕድገት አጸደ ሕጻናት ምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ነው ድምጽ የሰጡት።
ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!
#አሚኮ_ዜና #7ኛው_ምርጫ_2018_ዓ.ም #አዲስ_አበባ...
“ሀገራዊ ኀላፊነቴን ተወጥቻለሁ” አካል ጉዳተኛው መራጭ
ደብረ ታቦር: ግንቦት 24/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በደብረ ታቦር ከተማ ልጅ ያዘሉ እናቶች፣ አካል ጉዳተኞች እና ነዋሪዎች ድምጽ እየሰጡ ነው።
አቶ በለጠ ሞሳ አካል ጉዳተኛ ናቸው። አካል ጉዳተኛ መኾናቸው ግን በጠዋት ተነስተው ድምጽ ከመስጠት አላገዳቸውም።
ያለማንም ጣልቃ...








