የጽናት ቀን በአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ ጽሕፈት ቤት ተከበረ።
አዲስ አበባ: ጳጉሜ 01/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በሀገር አቀፍ ደረጃ የጽናት ቀን ኾኖ የተሰየመው የ2017 ዓ.ም ጳጉሜ 1 ቀን የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር የሰላም እና ፀጥታ ቢሮ ኀላፊ ሊዲያ ግርማ በተገኙበት ታስቧል።
ዕለቱ በመከላከያ ሠራዊት፤ በፌዴራል...
“በሁሉም ዘርፎች በምናደርገው ተጋድሎ የኢትዮጵያን መሠረት እናጸናለን” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር)
ባሕር ዳር: ጳጉሜን 01/2017 ዓ.ም (አሚኮ)ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) የጽናትን ቀን አስመልክተው መልእክት አስተላልፈዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልእክት ኢትዮጵያ ብልጽግናዋን የምታረጋግጠው መሠረቷን ለማጽናት በሚችሉ ብርቱ እጆች ነው ብለዋል።
በሁሉም ዘርፎች በምናደርገው ተጋድሎ...
“ፈተናዎችን በፅናት በማለፍ ዐዲስ ታሪክ የሚሠሩ ጀግኖች ሀገር ናት፤ ኢትዮጵያ” የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት
ባሕር ዳር: ጳጉሜን 01/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ጳጉሜን አንድ የሚከበረውን የጽናት ቀን አስመልክቶ መልእክት አስተላልፏል።
ፅኑ መሠረት፣ ብርቱ ሀገር!
በቀደምቶቻችን ደም እና አጥንት ፀንታ የኖረች ሀገራችንን በላቀ ደረጃ ታፍራ እና ተከብራ እንድትቀጥል የዐዲስ ምዕራፍ...
“በአብሮነት እና በኅብረት ተሰልፈን ሰላማዊ ዓድዋን በሕዳሴው ግድብ እውን አድርገናል” አረጋዊ በርሄ (ዶ.ር)
አዲስ አበባ: ነሐሴ 30/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅን በማስመልከት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት የፓናል ውይይት እያካሄደ ነው።
የፓናል ውይይቱ "በኅብረት ችለናል"በሚል መሪ መልእክት ነው እየተካሄደ የሚገኘው።
በውይይቱ መልእክት ያስተላለፉት የታላቁ...
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ደሴ ዲስትሪክት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ ወገኖች ማዕድ አጋራ።
ደሴ፡ ነሐሴ 30/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ደሴ ዲስትሪክት የ2018 ዓ.ም የዘመን መለወጫ በዓልን አስመልክቶ ለአቅመ ደካማ ወገኖች ማዕድ አጋርቷል።
አሚኮ ያነጋገራቸው ድጋፍ የተደረገላቸው ወገኖች በዓሉን በደስታ ለማሳለፍ እንደሚያግዛቸው ተናግረዋል። ለተደረገላቸው ድጋፍም ምሥጋናቸውን አቅርበዋል።
በኢትዮጵያ...








