የከተራ በዓል በሰሜን ጎንደር ዞን ደባርቅ ከተማ በድምቀት እየተከበረ ነው።

ደባርቅ: ጥር 10/2016 ዓ.ም (አሚኮ)በደባርቅ ከተማ በሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ የሚገኙ ታቦታት ከመንበራቸው ወጥተው ወደ ጥምቀተ ባህሩ እየወረዱ ይገኛሉ። በዓሉን የሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች በመዝሙር፤ የከተማው ታዳጊዎች እና ወጣቶች በባሕላዊ ጨዋታ አድምቀውታል። ዘጋቢ፦አድኖ ማርቆስ ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

“ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ!” አቶ ይርጋ ሲሳይ

ባሕር ዳር: ጥር 10/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ይርጋ ሲሳይ እንዳሉት የጥምቀት በዓል በመተሳሰብ፣ በፍቅርና በሠላም የምናከብረው፣ ከመለያየት ይልቅ በአንድነት፣ እርስ በእርስ ከመፎካከር ወጥተን በወንድማማችነት በኅብር አብረን የምንደምቅበት...

“በአማራ ክልል ያጋጠመው የጸጥታ ችግር ዘላቂ መፍትሔ እንዲያገኝ በጋራ መቆም ያስፈልጋል” ድረስ ሳህሉ (ዶ.ር)

ደብረ ማርቆስ: ጥር 10/2016 ዓ.ም (አሚኮ)በአማራ ክልል ለወራት ያጋጠመውን የጸጥታ ችግር በመፍታት የተገኘውን አንጻራዊ ሰላም ዘላቂነት በማረጋገጥ ሕዝቡ የተረጋጋ ሕይወትን እንዲመራ ዓላማ ያደረገ ውይይት በደብረ ማርቆስ ከተማ ተካሂዷል። በክልሉ ለወራት ያጋጠመው ችግር መፍትሔ እንዲያገኝ ነገሮችን...

የጥምቀት ዋዜማ የከተራ በዓል በእንጅባራ ከተማ በተለያዩ ሃይማኖታዊ ሥነ-ሥርዓቶች በድምቀት እየተከበረ ነው።

እንጅባራ: ጥር 09/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች ትህትናን ለማስተማር ሲል በፍጡሩ በዮሐንስ እጅ በዮርዳኖስ ወንዝ ዝቅ ብሎ መጠመቁን አብነት በማድረግ በየዓመቱ በልዩ መንፈሳዊ ሥነ-ሥርዓት የሚከበረው የጥምቀት ዋዜማ የከተራ በዓል በእንጅባራ ከተማ በእምነቱ...

“ከተራ የትህትና አንዱ መገለጫ በዓል ነው” ሊቀ ጉባኤ መጋቢ ሳሙኤል እንየው

ባሕር ዳር: ጥር 10/2016 ዓ.ም (አሚኮ)በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሀዶ ቤተ ክርስቲን ሥርዓት እና ትውፊት መሰረት ጥር 10 ቀን የከተራ በዓል ይከበራል፡፡ ስለ በዓሉ ሃይማኖታዊ እና ታሪካዊ ዳራ በበዓሉ መደረግ ስላለበት ጉዳይ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ዘርዘር ያለ...