
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ የአማራ እና የኦሮሞ ሕዝቦች በጋብቻ፣ በፖለቲካዊ ትሥሥር እና በባሕላዊ መስተጋብር ለዘመናት የተሳሰሩ የሀገር ግንባታ ዋልታዎች መኾናቸውን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሸዋና የይፋት ሡልጣኔቶችን እንዲሁም የጎንደር፣ የየጁ እና የወረ ሂመኑ ሥርወ መንግሥታትን ታሪክ በማስታወስ ሕዝቦቹ በታሪክ አብረው ሲዘምቱ፣ ሲያለሙ እና አብረው ሲዋጉ የኖሩ መኾናቸውን አብራርተዋል።
ዘመናዊት ኢትዮጵያን መፍጠር ከእነዚህ ሕዝቦች ውህደት ውጭ እንደማይቻል የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ “አጼ ምኒልክን ያለ ራስ ጎበና፣ ራስ ጎበናንም ያለ አጼ ምኒልክ ማሰብ አይቻልም” ብለዋል።
እንዲሁም ኢትዮጵያውያን በጋራ የሚኮሩበት የዓድዋ ድል ለአንዲት ሀገር የጋራ ሕልውና በጋራ የተከፈለ መስዋዕትነት እና የዚሁ ውህደት ትልቁ ማሳያ መኾኑንም አንስተዋል።
#Ameco #AbiyAhmed #Amhara_Oromo_Unity #EthiopianHistory
#ባሕር_ዳር #ሐምሌ_24_2018_ዓ_ም
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
