የአማራ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 12ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው። በጉባኤው የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምን ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ሪፖርት እያቀረቡ ነው ።

የ2018 በጀት ዓመት የትምህርት አፈጻጸምን በተመለከተ በሪፖርቱ ከተነሱ ጉዳዮች መካከል፦

በክልሉ የ6ኛ፣ የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል የተማሪዎችን ፈተና በስኬት ማጠናቀቅ ተችሏል።

በ12ኛ ክፍል ፈተና ከ59 ሺህ በላይ ተማሪዎች በበይነ መረብ (ኦንላይን) ፈተናውን ወስደዋል።

በትምህርት ለትውልድ ኢኒሼቲቭ 233 አዲስ ትምህርት ቤቶች ተገንብተዋል።

በበጀት ዓመቱ 4 ሚሊዮን 410 ሺህ 954 ተማሪዎች ተመዝግበዋል።

የ2018 በጀት ዓመት የጤና አፈጻጸምን በተመለከተ በሪፖርቱ ከተነሱ ጉዳዮች መካከል፦
የክልሉን ማኅበረሰብ ጤናማ እና አምራች ለማድረግ፤ ተደራሽ እና ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ለመሥጠት በርካታ ሥራዎች መከናወናቸው ተገልጿል።

የእናቶች እና ሕጻናት ጤና አጠባበቅን ማሻሻል፤ ተላላፊ እና ተላላፊ ያልኾኑ በሽታዎችን መከላከል እና በሌሎች ዘርፎችም መሠራቱ ተነስቷል።

የመጀመሪያ ደረጃ የቅድመ ወሊድ ለ872 ሺህ 441 እናቶች እና የአራተኛ ደረጃ ቅድመ ወሊድ አገልግሎት ከ789 ሺህ በላይ ለኾኑ እናቶች ተሰጥቷል።

በወሊድ ወቅት የአተነፋፈስ ችግር ላጋጠማቸው 12 ሺህ 330 ሕጻናትም ድጋፍ ተደርጓል።

ለ821 ሺህ 949 ሕጻናት የኩፍኝ መከላከል ክትባት ተሠጥቷል።

1 ሚሊዮን 387 ሺህ 155 ለሚኾኑ በወባ ለተጠቁ የማኅበረሰብ ክፍሎች ሕክምና መስጠት ተችሏል።

ከ18 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ መድኃኒቶችን እና የሕክምና መሣሪያዎችን ለጤና ተቋማት ማሰራጨት ተችሏል።

በደም ባንኮች 76 ሺህ 498 ዩኒት ደም ተሠብሥቧል።

4 ሚሊዮን 177 ሺህ 591 የማኅበረሰብ አቀፍ ጤና መድኀን አባላትን ማፍራት ተችሏል። ከዚህም 6 ቢሊዮን 626 ሚሊዮን 110 ሺህ ብር በላይ ገቢ ማግኘት መቻሉ በሪፖርቱ ተጠቅሷል።