የአማራ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 12ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል። በጉባኤው የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምን ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ሪፖርት እያቀረቡ ነው ።

የ2018 በጀት ዓመት የቱሪዝም ልማትን በተመለከተ በሪፖርቱ ከተነሱ ጉዳዮች መካከልም፦

250 የቋሚ ቅርሶችን የጉዳት መጠን በደረጃ መለየት ተችሏል።

ለ1ሺህ 43 ቅርሶች ጥገና ተከናውኗል።

18 የተዘረፉ ቅርሶችን ማስመለስ ተችሏል።

ስድስት የቱሪዝም መዳረሻ ቦታዎችን በካርታ፤ በጂፒኤስ እና ጎግል ላይ ተደራሽ ማድረግ መቻሉ ተጠቅሷል።

ለቱሪዝም መዳረሻዎች 594 ኪሎ ሜትር መንገድ ተሠርቷል።

10 ኢኮ-ሎጅ እና ሪዞርቶች፤ 77 ሆቴሎች እና 10 ባሕላዊ ሬስቶራንቶች መገንባታቸው በርእሰ መሥተዳድሩ
ሪፖርት ተነስቷል።