
አሁን ግን ኢትዮጵያ በታሪኳ አይታው በማታውቀው መልኩ ሰፊ የሕዝብ ስብጥርን ያቀፈ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ እያካሄደች ትገኛለች። ይህ መድረክ የቆየውን ጎጂ አካሄድ በመስበር ለአዲስ የፖለቲካ ባሕል መሠረት እየጣለ ነው።
ይህም የሀሳብ የበላይነትን በመሳሪያ የመጫን ባሕልን እንደሚያስቀር ገልጸዋል። በምትኩ ልዩነቶችን በሀሳብ እና በምክክር የመስማማት የፖለቲካ ባሕልን የሚተክል መኾኑንም ነው ያስረዱት።
በካሊፎርኒያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህሩ ፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያም የምክክሩ ትልቁ ስኬት የሚለካው በሚወጡት ሰነዶች ብቻ ሳይኾን ሕዝቡ እርስ በእርሱ እንዲነጋገር እና የሌላውን ወገን እይታ እንዲረዳ በመደረጉ ነው ብለዋል።
ምክክሩ የተለመደውን የሊህቃንን የበላይነት በማስወገድ በቀጥታ ወደ ሕዝብ ተሳትፎ ያመራ ዘመናዊ የግጭት አፈታት መንገድ መኾኑን አብራርተዋል።
በዚህ የታሪካዊ ጉባኤ አካል ለመኾን በመቻላቸው ትልቅ ክብር እና ኩራት እንደተሰማቸውም ገልጸዋል።
“ላለፉት 40 እና 50 ዓመታት በጠበቃነት፣ በማስተማር፣ በጋዜጠኝነት እና በተሟጋችነት ያሳለፍኩት ሕይወት ‘እኔ ካላሸነፍኩ’ የሚል የዜሮ ድምር ፖለቲካ ነበር” የሚሉት ፕሮፌሰሩ “አሁን ግን የሁሉንም አሸናፊነት በሚያረጋግጠው የ4 ሺህ አባላቱ የምክክር ጉባኤ ቡድን አካል በመኾን ትልቅ ዕድል አግኝቻለሁ” ብለዋል።
በዓይነቱ ልዩ የኾነው ይህ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ኢትዮጵያን ለዘመናት አስረው ከያዟት የታሪክ እና የፖለቲካ ውዝግቦች አውጥቶ ወደ አዲስ የሰላም እና የልማት ምዕራፍ የሚያሸጋግር “የንጋት ወጋገን” ተደርጎ የሚወሰድ ነው።
በመድረኩ የሚደመጡት 4 ሺህ ድምጾችም የብዙ ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን ምኞት፣ ተስፋ እና ስጋት ይዘው በመቅረብ ሀገሪቱን ከግጭት ፖለቲካ ወደ ውይይት እና ይቅር ባይነት የሚያሸጋግር ጠንካራ መሠረት እንደሚጥል ተስፋ ተጥሎበታል።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
