
በዕለቱ በምክር ቤት አባላት ከተነሱ ዋና ዋና ጥያቄዎች መካከል:-
👉 ሀገራዊ ምክክሩ የታለመለትን ዓላማ እንዲያሳካ መንግሥት ምን አይነት የሎጀስቲክስ፣ የፖለቲካ እና ተቋማዊ ድጋፍ እያደረገ ነው?
👉 ምክክሩ ያለመሰናክል እንዲሳካስ ከእያንዳንዱ ዜጋ ምን አይነት ኀላፊነት ይጠበቃል?
👉 ተጀምረው የተጓተቱ እና ያልተጠናቀቁ ትላልቅ ፕሮጀክቶች እና ታቅደው ላልተጀመሩ ፕሮጀክቶች ምን የታሰበ ነገር አለ?
👉 በልማት ፕሮጀክቶች ተነሺ ለኾኑ የማኅበረሠብ ክፍሎች ተገቢውን ማቋቋሚያ እንዲሠጣቸው በማድረግ በኩል ምን የተቀመጠ አቅጣጫ አለ?
👉 በኑሮ ውድነት፣ በቤት ችግር እና በገቢ ማነስ ለተቸገሩ የመንግሥት ሠራተኞች እና ለዝቅተኛ ነዋሪ የኅብረተሰብ ክፍሎች ኑሮውን ለማሻሻል ምን የታሰበ ነገር አለ? አዲስ ከሚመሠረተው መንግሥት ምን ይጠበቃል?
👉 በአዲስ አበባ የተጀመረው የተማሪ ምገባ መርሐ ግብር ወደ ሌሎች ክልሎች እንዲሰፋ ለክልሎች አስገዳጅ ኾኖ ቢቀርብ?
👉 የኦዲት ጉድለት የሚገኝባቸው ተቋማት አሥፈጻሚዎች ለምን ተጠያቂ አይኾኑም? መንግሥት እንዴት ሊያስተካክለው አስቧል?
👉 የወደብ ጉዳይ የሉዓላዊነት ጉዳይ ነው ተብሎ ሢሠራ ቆይቷል፤ በመንግሥት በኩል አሁን ላይ ምን ደረጃ ላይ እንዳለ ማብራሪያ ቢሰጥ?
የሚሉ ጥያቄዎች ተነስተዋል።
#የሕዝብ_ተወካዮች_ምክር_ቤት #ኢትዮጵያ #ሀገራዊ_ምክክር #ዘላቂ_ሰላም #የኑሮ_ውድነት #ልማት_ፕሮጀክቶች #የኦዲት_ተጠያቂነት #የወደብ_ጉዳይ #AMECO #አሚኮ
#ባሕርዳር_ሰኔ_30_2018ዓ_ም
በአሰፋ ልጥገበው
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
