
ባሕር ዳር፡ ሰኔ 20/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መሥኮች ሲያሠለጥናቸው የቆዩ 6 ሺህ 492 ተማሪዎችን ያስመርቃል።
ከተመራቂዎች መካከል 1 ሺህ 691 የሚኾኑት ሴቶች እንደኾኑ ከዩኒቨርሲቲው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ዩኒቨርሲቲው በአሁኑ ሰዓት ከ109 ዓለም አቀፍ እና 127 ሀገር አቀፍ በድምሩ ከ236 አጋር አካላት ጋር በትብብር ይሠራል።
ቁጥራቸው 152 የሚኾኑ ዓለም አቀፍ ተማሪዎችን በማስተማር ላይም ይገኛል።
#አሚኮ #አሚኮዜና #ባሕርዳር #Bahirdar #bahirdaruniversity # ባሕርዳርዩኒቨርሲቲ #graduation #Ethiopia
በሮዛ የሻነህ
