
ባሕር ዳር: ሰኔ 17/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በቅርቡ የበረራ አገልግሎት የጀመረው የደብረ ማርቆስ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎቱን በማሳደግ ላይ ይገኛል። ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ፦
✈️ ከአዲስ አበባ ወደ ደብረ- ማረቆስ ደርሶ መልስ በየቀኑ
✈️ ከደብረ ማርቆስ ወደ ባሕር ዳር በሳምንት አራት ቀናት (ሰኞ፣ ረቡዕ ፣ አርብ እና እሁድ )
✈️ከባሕር ዳር ወደ ደብረ ማርቆስ ደግሞ በሳምንት ሶስት ቀን (ማክሰኞ ፣ ሀሙስ እና ቅዳሜ) የበረራ አገልግሎት ሊሰጥ ነው።
ከሚቀጥለው አርብ ሰኔ 19/2018 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎቱ እንደሚጀምር ተገልጿል።
#አሚኮ #አማራ_ክልል #ኢትዮጵያ #የኢትዮጵያአየርመንገድ #ethiopianairlines #ባሕርዳር #ደብረማርቆ #አዲስአበባ
