ኢቫሪስት ንዲያሺሚዬ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ላኩ።

3

 

ባሕር ዳር፡ ሰኔ 17/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የቡሩንዲ ፕሬዚዳንት እና የአፍሪካ ኅብረት የወቅቱ ሊቀመንበር ኢቫሪስት ንዲያሺሚዬ በኢትዮጵያ በተካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ብልጽግና ፓርቲ ያገኘውን ድል አስመልክተው ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የእንኳን ደስ አለዎት መግለጫ አስተላልፈዋል።

ፕሬዚዳንት ኢቫሪስት ንዲያሺሚዬ “የተከበሩ ወንድሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) እና ብልጽግና ፓርቲ በምርጫው ላስመዘገቡት ስኬታማ ውጤት በአፍሪካ ኅብረት እና በቡሩንዲ ሪፐብሊክ ስም የተሰማኝን ልባዊ ደስታ እገልጻለሁ” ብለዋል።

#አሚኮ #አሚኮዜና #PrimeMinister #AbiyAhmed #ኢትዮጵያ

Previous articleየሰቆጣ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤትን ለመጭው የ2019 የትምህርት ዘመን ለማድረስ በትኩረት እየተሠራ ነው።
Next articleሩሲያ ለሰላም ንግግር ዝግጁነቷን አስታወቀች።