ለሳይበር ጥቃት ሰለባ የኾኑ ታዳጊዎች ምን የተለየ ባህሪ ያሳያሉ?

7

 

ባሕር ዳር: ሰኔ 01/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ✍️ራስን ማግለል እና ከመጠን ያለፈ ሚስጥራዊነት፦

-በርን ዘግቶ ለረጅም ሰዓታት ስልክ ወይም ኮምፒውተር መጠቀም
-ስልኩን ሌላ ሰው እንዳይዝባቸው መሳቀቅ ወይም መቆጣት
-ኦንላይን ላይ የሚያወራቸውን ሰዎች ማንነት በሚስጥር መያዝ

✍️ማኅበራዊ ለውጦች፦

-ከቀድሞ ጓደኞች፣ ከቤተሰብ ጨዋታዎች እና ግንኙነቶች ሙሉ በሙሉ መራቅ
-በትምህርት ላይ ፍላጎት ማጣት እና ውጤት መቀነስ።

✍️ስሜታዊ እና ሥነ-ልቦናዊ ለውጦች፦

-ያለምንም ግልጽ ምክንያት በድንገት መበሳጨት፣ ቶሎ ማልቀስ ወይም ፍጹም ዝምተኛ መኾን
-ስልክ ከተጠቀሙ በኋላ ከፍተኛ ፍርሃት፣ ጭንቀት እና የጥፋተኝነት ስሜት ማሳየት
-የምግብ ፍላጎት መቀነስ፣ እንቅልፍ ማጣት እና በሕልም መቃዠት።

✍️እነዚህ ምልክቶች በታዳጊዎች ላይ ከታዩ በተረጋጋ ስሜት ቀርቦ ማናገር እንደሚመከር የኢንሳ መረጃ ይገልጻል።

የአሚኮ ዲጅታል ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/Amharamediacorporations

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ በኮምቦልቻ ከተማ የሚገኙ ኢንዱስትሪዎችን ጎበኙ።
Next articleየሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ተሳታፊዎች እነማን ናቸው?