
አዲስ አበባ: ግንቦት 29/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከድምጽ አሰጣጥ ሂደቱ ጀምሮ የምርጫውን ሂደት በመገናኛ ብዙሃን በኩል ለሕዝብ እያደረሰ ይገኛል።
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የውጤት ሂደቱን ተከትሎ ዛሬ በሰጠው መግለጫ የምርጫ ክልሎች የማዳመር ሥራ ላይ እንደሚገኙ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላተወርቅ ኃይሉ ተናግረዋል።
ከ1 ሺህ 138 የምርጫ ክልሎች ውስጥ 825 የምርጫ ክልሎች የማዳመር ሥራቸውን ማጠናቀቃቸውን ገልጸዋል።
29 የሚደርሱ የምርጫ ክልሎች ደግሞ ወደ ማረጋገጫ ሂደት መግባታቸውን ሰብሳቢዋ ተናግረዋል።
ዘጋቢ፦ ቴዎድሮስ ኃይለኢየሱስ
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/Amharamediacorporations
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
