“ምርምሮች የማኅበረሰቡን ችግር የሚፈቱ መኾን አለባቸው”

17

 

ጎንደር: ግንቦት 28/2018 ዓ.ም (አሚኮ) 32ኛው ሀገር አቀፍ ዓመታዊ የምርምር ጎባኤ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው።

‎በጉባኤው የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጅ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ.ር)፣ የአፍሪካ ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት ዛዲግ አብርሃ፣ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አሥራት አጸደወይን (ዶ.ር)፣ የዩኒቨርሲቲው የሥራ ኀላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

‎ጉባኤውን የከፈቱት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አሥራት አጸደወይን (ዶ.ር) ዩኒቨርሲቲው በጤናው እና ሌሎች ዘርፎች በቴክኖሎጅ የታገዘ የምርምር ተግባር እያከናወነ መኾኑን አንስተዋል።

ዩኒቨርሲቲው ‎ከመማር ማስተማር ባሻገር የማኅበረሰብ አቀፍ አገልግሎት እየሰጠ ነውም ብለዋል።

የአፍሪካ ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት ዛዲግ አብርሃ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚያወጧቸው ምርምሮች የማኅበረሰብን ችግር መነሻ ያደረጉ ሊኾኑ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

‎ምርመምሮች ከቴክኖሎጅ ጋር የሚጣጣሙ ሊኾኑ ይገባልም ነው ያሉት።

‎ምርምሮች የዲጂታል 2030ን ግብ እውን የሚያደርጉ እና የሚያግዙ ሊኾኑ እንደሚገባ የተናገሩት ደግሞ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጅ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ.ር) ናቸው።

‎የሚሠሩ ምርምሮች ወደ ተግባር የሚቀየሩ እና የማኅበረሰቡን ችግር የሚፈቱ መኾን እንዳለባቸውም አንስተዋል።

#አሚኮ_ዜና #ምርምር_”ጎንደር_ዩኒቨርሲቲ #አማራ_ክልል #ኢትዮጵያ

ዘጋቢ:- አዲስ ዓለማየሁ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/Amharamediacorporations

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየአርሶአደሮችን የምርት አቅም ለመጨመር በኩታ ገጠም የማደራጀት ሥራ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ ነው።
Next article🚫ታዳጊዎችን ዒላማ ያደረጉ አደገኛ የሳይበር ጥቃቶች፦