
ደብረብርሃን፡ግንቦት 24/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) እና የአርጎባ አንድነት ጀበርቲን ፓርቲን በመወከል ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሚወዳደሩ ዕጩዎች በተለያዩ ምርጫ ጣቢያዎች በመገኘት ድምፃቸውን ሰጥተዋል።
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ፓርቲን በመወከል ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሚወዳደሩት ረዳት ፕሮፌሰር ዳምጠው ተሰማ ፤ እሳቸው በሚወዳደሩበት አካባቢ ሂደቱ ሰላማዊ በኾነ መልኩ እየተከናወነ እንደኾነ ተናግረዋል።
በተመሳሳይ የአርጎባ አንድነት ጀበርቲ ፓርቲን በመወከል ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እየተወዳደሩ የሚገኙት ሀያት ኡስማን በሰጡት አስተያየት የምርጫው ሂደት ፍጹም ሰላማዊ በኾነ መልኩ እየተካሄደ መኾኑን መታዘባቸውን ገልጸዋል።
ዘጋቢ:- ደጀኔ በቀለ
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
