“የምመርጠው ጠባቂ እንዲኖረኝ ነው” የ95 ዓመቱ የእድሜ ባለጸጋ

4
🇪🇹🗳️
ደብረብርሃን: ግንቦት 24/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በደብረብርሃን ከተማ ድምፃቸውን ከሰጡት መካከል የ95 ዓመቱ የዕድሜ ባለጸጋ ጋሽ ብዙነህ መሐመድ አንዱ ናቸው።
‎እኝህ አባት ዕድሜያቸው ሳይበግራቸው ወደ ምርጫ ጣቢያ ያቀኑት የምርጫ እና የመሪ አስፈላጊነት በጥልቅ በመረዳታቸው ነው።
‎”እኔ እምመርጠው ጠባቂ እንዲኖረኝ ነው” ብለዋል፡፡
‎ጋሽ ብዙነህ ድምፃቸውን በካርዳቸው ከሰጡ በኋላ በሀገር ውስጥ እና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በሙሉ ለሀገር ዕድገት እና ለሰላም በትጋት እንዲቆሙ አባታዊ ምክራቸውን አስተላልፈዋል።
ዘጋቢ፦ደጀኔ በቀለ
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous article“ምርጫ ለአንድ ሀገር የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ መሠረት ነው” የከሚሴ ከተማ ነዋሪዎች
Next articleየኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን በአዲስ አበባ የምርጫ ጣቢያዎችን ተዘዋውረው እየተመለከቱ ነው።