“የዛሬው አሻራችን ለራሳችን ብቻ ሳይኾን ለልጆቻችንም ትልቅ ትርጉም ያለው ነው” እናቶች

10
ደብረ ብርሃን፡ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በደብረ ብርሃን ከተማ አሥተዳደር እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ 08 ቀበሌ ምርጫ ጣቢያ ድምጻቸውን ከሰጡ መራጮች መካከል ወይዘሮ ዘውዴ መኮንን አንዷ ናቸው።
‎የዛሬው አሻራቸው ለራሳቸው ብቻ ሳይኾን ለልጆቻቸው ትልቅ ትርጉም እንዳለው በጽኑ እንደሚያምኑ ተናግረዋል።
‎”በምርጫው መሳተፍ ለእኔም፣ ለልጆቼም፣ ለሀገሬም የማይተካ ሚና አለው ብለዋል። በተለይም ለልጆቼ ሰላሟ የተጠበቀ ሀገር ለማስረከብ የዛሬው ድምጼ ትልቅ ዋጋ አለው” ነው ያሉት።
‎ምርጫ የዜግነት መብት ብቻ ሳይኾን ለትውልድ የሚቀመጥ የተስፋ መሠረት ጭምር ነው ያሉት ደግሞ ወይዘሮ ቀለሟ ስመኝ ናቸው።
‎እናቶች ለልጆቻቸው የተሻለች ኢትዮጵያን ለማስረከብ ዛሬ ላይ ድምጻቸውን እንዲሰጡም መክረዋል።
#Ethiopian-electio #ኢትዮጵያ-ትመርጣለች
ዘጋቢ፦ ደጀኔ በቀለ
የአሚኮ ዲጂታል ቤተሰብ ይሁኑ !
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን !
Previous articleምርጫውን አፍሪካውያን መታዘባቸው ኢትዮጵያ የፓን አፍሪካኒዝም ፈር ቀዳጅነቷን ዳግም በዴሞክራሲያዊ ምርጫ የደገመችበት ነው።
Next article