6
🇪🇹🗳️ጎንደር፡ግንቦት 24/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ‎የኅብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እጩ መኮንን ብርሃን በጎንደር ከተማ ተገኝተው ድምጻቸውን ሰጥተዋል።
‎ካርዳቸውን አባ ሳሙኤል ቀበሌ አየር ማረፊያ ምርጫ ጣቢያ ማውጣታቸውን የገለጹት አቶ መኮንን ድምጻቸውንም በዚሁ ምርጫ ጣቢያ ተገኝተው መስጠታቸውን ገልጸዋል።
‎በተገኙበት የምርጫ ጣቢያ መራጮች ከማለዳው ጀምሮ ይበጀናል፣ ያስተዳድረናል ያሉትን እየመረጡ መኾናቸውን አንስተዋል።
‎የድምጽ አሰጣጥ ሂደቱ ሰላማዊ በኾነ መንገድ እየተከናወነ መኾኑን መታዘባቸውንም አመላክተዋል።
‎ምርጫ ሰላማዊ መንግሥት ለመመስረት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነውም ብለዋል። መራጩ ሕዝብ የሰጠውን ድምጽ በጸጋ ተቀብሎ የዴሞክራሲ ሥርዓትን መለማመድ ይገባልም ነው ያሉት።
‎ሀገርን ለማስቀጠል ኀላፊነትን መወጣት እንደሚጠበቅም ገልጸዋል። ሕዝብ የሰጠውን ድምጽ መቀበል አማራጭ ብቻ ሳይኾን ግዴታ መኾኑንም ጠቁመዋል።
ዘጋቢ:- ደስታ ካሣ
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous article“የዛሬው አሻራችን ለራሳችን ብቻ ሳይኾን ለልጆቻችንም ትልቅ ትርጉም ያለው ነው” እናቶች
Next article🇪🇹🗳️ ዜጎች በምርጫ መንግሥት ለመመስረት ያላቸው ቁርጠኝነት የሚደነቅ መኾኑን በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ።