ዜናኢትዮጵያየእለቱ አበይት ዜና “ምርጫ መሪህን በሰላም የምትመርጥበት መንገድ ነው” የ90 ዓመት ዕድሜ ባለጸጋ June 1, 2026 9 አዲስ አበባ፡ግንቦት 24/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በአዲስ አበባ በቦሌ ክፍለ ከተማ ምርጫ ክልል 17 ወረዳ 13 ላስታ ሥላሴ የምርጫ ጣቢያ መርጠው ሲወጡ አሚኮ ያገኛቸው የ90 ዓመት ዕድሜ ባለጸጋ “ምርጫ መሪህን በሰላም የምትመርጥበት መንገድ ነው” ብለዋል። የዕድሜ ባለጸጋዋ ለ5ኛ ጊዜ ምርጫ እንደመረጡም ነግረውናል። ምርጫ መብት በመኾኑ በአግባቡ መጠቀም ይገባል ነው ያሉት። #አሚኮ_ዜና #7ኛው_ምርጫ_2018_ዓ.ም #አዲስ_አበባ #አማራ_ክልል #ኢትዮጵያ ዘጋቢ፦አንዱዓለም መናን የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ! https://linktr.ee/Amharamediacorporations ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን! ተዛማች ዜናዎች:"ለሀገር ዕድገት እና ልማት ስንል በምርጫው ተሳትፈናል" መራጮች