
ከዚህ በፊት በሁለት የምርጫ ጊዜያቶች መሳተፋቸውንም ገልጸዋል። በዛሬው ምርጫ ለቀጣዩ ትውልድ የሚበጅ መንግሥትን ለመምረጥ በምርጫው መሳተፋቸውንም ነው የተናገሩት።
ሌላው በምርጫው ላይ ሲሳተፉ ያገኘናቸው አቶ ምናለ ታረቀኝ አካል ጉዳተኛ መኾናቸው ምንም ሳይገድባቸው ይኾነኛል እና ያስተዳድረኛል የሚሉትን ለመምረጥ በምርጫ ጣቢያ መገኘታቸውን ተናግረዋል።
በምርጫው ለአካል ጉዳተኞች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ስል ድምጼን ሰጥቻለሁም ብለዋል።
ሌሎች አካል ጉዳተኞችም ያወጡትን ካርድ በመጠቀም የሚበጃቸውን መምረጥ እንዳለባቸው ነው የተናገሩት።
ማኅበረሰቡ በምርጫው ከመሳተፍ ባለፈ ዘላቂ ሰላም እንዲመጣ መሥራት እንደሚገባውም ተናግረዋል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን
