
ከእነዚህ መራጮች መካከል ከ95 ዓመት በላይ ዕድሜ ያላቸው ጴጥሮስ ዋነኛው አንዱ ናቸው። ከዚህ ቀደም በነበሩ ምርጫዎች ላይ መሳተፋቸውንም አስታውሰዋል።
በዘንድሮው ምርጫ በመሳተፋቸው እና የሚያምኑበትን በመምረጣቸው ደስተኛ መኾናቸውን ገልጸዋል። የዕድሜ ባለጸጋው ያመኑበትን አካል መምረጣቸውንም ተናግረዋል።
ምርጫ የሕዝብን ዕውነተኛ ውሳኔ ለማሳየት እና ለማወቅ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጸዋል። ዜጎች በምርጫ በመሳተፍ የዜግነት መብታቸውን እንዲጠቀሙ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በስማቸው አጥናፍ
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
