
ፍኖተ ሰላም: ግንቦት 24/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የቡሬ ከተማ ነዋሪዎች ድምፃቸውን እየሰጡ ይገኛሉ። በምርጫው አካል ጉዳተኞች እየተሳተፉ ነው።
ለአሚኮ አስተያየታቸውን የሰጡት ፍሬው አልማው እና ወንድሙ ታደሰ ምርጫው እስኪደርስ በጉጉት ሲጠብቁ መቆየታቸውን አንሰተዋል። ”እኛ አካል ጉዳተኞች በሀገር ላይ ድርሻ ስላለን የምንፈልገውን ፓርቲ መርጠናል” ብለዋል።
በቀጣይም ከሚመሠረተው መንግሥት ጎን በመኾን የበኩላቸውን እንደሚወጡ ነው የጠቆሙት።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
