
ባሕር ዳር: ግንቦት 24/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በደብረ ታቦር ከተማ ፋርጣ አንድ ምርጫ ክልል ነዋሪዎች ድምጽ እየሰጡ ነው።
ወጣቶች፣ አካል ጉዳተኞች፣ ሴቶች እና አረጋውያን በምርጫው እየተሳተፉ ነው።
በከተማዋ ሁለት ምርጫ ጣቢያ ውኃ አገልግሎት “ለ” አንድ ላይ ድምፅ ሲሰጡ ያገኘናቸው የእድሜ ባለጸጋዋ ወይዘሮ አሰፉ ደርሴ በሌሊት ቤተ ክርስቲያን ደርሰው እግረ መንገድ ድምፅ ለመስጠት መምጣታቸውን ነግረውናል። መራጯ ቤተ ክርስቲያን ሄጄ የፀለይኩት ለሀገር ሰላም፣ ድምፄን የሰጠኹትም ለሀገር ሰላም ነው ብለዋል።
ከዚህ በፊትም በተደጋጋሚ በምርጫ መሳተፋቸውን የነገሩን አዛውንቷ “ከብት ያለ እረኛ፣ ሰው ያለ ዳኛ አይኖርም ብየ ዘንድሮም የሚበጀውን መርጫለሁ” ነው ያሉት።
ዘጋቢ፦ አድኖ ማርቆስ
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
