ለ7ኛ ጊዜ በምርጫ የሚሳተፉት የዴሞክራሲ ሕያው ምስክር እናት።

9
🇪🇹🗳️
ደብረብርሃን፡ግንቦት 24/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ዛሬ በኢትዮጵያ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እየተካሄደ ይገኛል።
በዚህ ታሪካዊ ቀን ልዩ ታሪክ ካላቸው መራጮች መካከል የደብረብርሃን ከተማ ነዋሪዋ ወይዘሮ የሸዋጣይ ነጋሽ አንዷ ናቸው።
‎​ወይዘሮ የሸዋጣይ በሀገሪቱ ድምጽ መስጠት ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ከአንድም ምርጫ ቀርተው አያውቁም።
‎ዛሬም ማለዳ ተነስተው ወደ ምርጫ ጣቢያ ያቀኑት እኚህ አንጋፋ መራጭ “ይበጀኛል፣ ይጠቅመኛል” ላሉት እና ላመኑበት ድምጻቸውን በነፃነት ሰጥተዋል።
‎​”ድምፄ ዋጋ አለው፤ የሀገርን እጣ ፈንታ ይወስናል። ለዛ ነው በየጊዜው ላመንኩበት ፓርቲ ድምፄን የምሰጠው” ይላሉ ወይዘሮ የሸዋጣይ።
‎​ምርጫ የነገን እጣ ፈንታ በራስ እጅ የመወሰን መብት እና ኀላፊነት መኾኑን በተግባር ያሳዩት ወይዘሮ የሸዋጣይ ኅብረተሰቡ በምርጫው በንቃት እንዲሳተፍ መልዕክት አስተላልፈዋል።
‎​በደብረብርሃን ምርጫ ክልል ውስጥ ልዩ ልዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች በምርጫው በንቃት እየተሳተፉ መኾኑን አሚኮ በምልከታው አረጋግጧል።
ዘጋቢ፦ደጀኔ በቀለ
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous articleልጃቸውን ለመገላገል በምጥ ስሜት ውስጥ ኾነው ድምጽ የሰጡት እናት።
Next article“ድምጼን የሰጠኹት ለሀገር ሰላም ነው” የዕድሜ ባለጸጋዋ እናት