
ከሚሴ፡ግንቦት 24/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ወይዘሮ ሳራ አህመድ በከሚሴ ከተማ የመተሆሮ ቀበሌ ነዋሪ ናቸው።
ወይዘሮ ሳራ ልጃቸውን ለመገላገል የምጥ ስሜት እየተሰማቸው ምጣቸውን ተቋቁመው ለሀገር ይበጃል ላሉት ድምጻቸውን ሰጥተዋል።
ሀገር እና ትውልድን ለማስቀጠል በሕዝብ የተመረጠ መንግሥት ያስፈልጋል ያሉት ወይዘሮ ሳራ።
ድምጻቸውን ለሚወክላቸው በመስጠታቸው ደስተኛ መኾናቸውን ተናግረዋል።
ድምጻቸውን ከሰጡ በኋላም ልጃቸውን ለመገላገል በመጡበት አምቡላንስ ወደ ከሚሴ ጠቅላላ ሆስፒታል አቅንተዋል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
