
ጎንደር፡ግንቦት 24/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በጠዋት ወጥተው ይበጀናል ላሉት ድምፃቸውን መስጠታቸውን በጎንደር ከተማ የምርጫ ክልል 2 መራጮች ተናግረዋል።
አሚኮ ያነጋገራቸው ወይዘሮ ህድጃ ጥጋቡ በጠዋት ወጥተው ይበጀኛል ላሉት ድምፃቸውን መስጠታቸውንም ነው የተናገሩት።
ሃሳባቸውን ያጋሩን ሌላኛው መራጭ አቶ መኮንን ተካልኝ ለሀገር ዕድገት ይበጃል ያሉትን መምረጣቸውን አንስተዋል።
ካርዳቸውን ተጠቅመው ሰላምን ለማጽናት መምረጣቸውን የነገሩን ደግሞ መሪጌታ ደሴ መኳንንት ናቸው።
አስተያየት ሰጭዎቹ በጠዋት ወጥተው በሰላማዊ መንገድ ድምጻቸውን መስጠታቸውንም አመላክተዋል።
መራጮቹ ምርጫ የሥልጡን ማኅበረሰብ መገለጫ መኾኑን በመረዳት ዜጎች ያወጡትን ካርድ በአግባቡ መጠቀም እንዳለባቸውም መክረዋል።
ዘጋቢ፦ደስታ ካሳ
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
