ለሰባተኛ ጊዜ በምርጫ የተሳተፉት መራጭ በኮምቦልቻ

8
🇪🇹🗳️ደሴ፡ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ሙሉጌታ ጌጡ ይባላሉ፤ የኮምቦልቻ ከተማ ነዋሪ ናቸው።
በኮምቦልቻ ከተማ ቦርከና ክፍለ ከተማ አየር ማረፊያ ቀበሌ አየር ማረፊያ ምርጫ ጣቢያ በመገኘት በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጻቸውን ሰጥተዋል።
ከ1987 ዓ.ም ጀምሮ በምርጫ በመሳተፍ ለሰባተኛ ጊዜ መምረጣቸውንም ተናግረዋል። ከስድስቱም ዙር በበለጠ ሰባተኛው ምርጫ ሰላማዊ እና ከአድሎ የጸዳ ኾኖ መመልከታቸውን ተናግረዋል።
ከሌሊቱ 11:00 ጀምሮ በምርጫ ጣቢያው በመገኘት ሰዓቱን ጠብቀው መምረጣቸውንም ገልጸዋል።
ዘጋቢ:- ያየህ ፈንቴ
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous articleለሰባተኛ ጊዜ የመረጡት የ90 ዓመት ባለጸጋዋ እናት
Next articleምርጫ የሥልጡን ማኅበረሰብ መገለጫ መኾኑን የጎንደር ከተማ መራጮች ተናገሩ።