በሰሜን ሸዋ ዞን ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት እንዲከናወን ቅድመ ዝግጅቱ ተጠናቅቋል።

8

 

​ደብረ ብርሃን: ግንቦት 23/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሰላሙ በተጠበቀ መልኩ ለመፈጸም አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን የሰሜን ሸዋ ዞን ሰላም እና ጸጥታ መምሪያ አስታውቋል።

​የመምሪያው ምክትል ኀላፊ ዓባይ ድሌ በሁሉም የዞኑ ወረዳዎች የጸጥታ አባላት ስምሪት ተሰጥቷቸዋል ብለዋል። የጸጥታ አካሉ በቁርጠኝነት ኀላፊነቱን እየተወጣ እንደኾነም ገልጸዋል።

በምርጫው ዕለት እና በድህረ-ምርጫው ሂደት አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን ማኅበረሰቡ የተለመደውን ንቁ ትብብር እና ድጋፍ እንዲያደርግም ጥሪ አቅርበዋል።

#አሚኮ_ዜና #ምርጫ_2018
#ሰሜን-ሸዋ #አማራ_ክልል #ኢትዮጵያ🇪🇹

​ዘጋቢ፦ ለዓለም ለይኩን

የአሚኮ ዲጅታል ቤተሰብ ይሁኑ !

https://linktr.ee/Amharamediacorporations

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን !

Previous article🗳️ 🇪🇹 ለሀገር እና ለሕዝብ ይጠቅማል ያሉትን ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን የአምበር ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።
Next articleምርጫው የሀገሪቱ የወደፊት መጻኢ ዕድል የሚወሰንበት ነው።