
ባሕር ዳር: ግንቦት 23/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚደረጉ ዝግጅቶች በየአካባቢው ተጠናክረው ቀጥለዋል።
የሰሜን ጎጃም ዞን ሰላም እና ጸጥታ መምሪያም ምርጫው ስኬታማ ኾኖ እንዲጠናቀቅ በቂ ዝግጅት ማድረጉን አስታውቋል።
የመምሪያው ኀላፊ ገብረ ሥላሴ ታዘብ የምርጫው ሂደት ደኅንነቱ የተጠበቀ እንዲኾን የዞኑ የጸጥታ ኃይል ከክልሉ እና ከፌዴራል የጸጥታ አካላት ጋር በመሆን በቅንጅት እየሠራ ነው ብለዋል።
በዞኑ በሚገኙ የምርጫ ክልሎች እና የምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ቁሳቁስ ያለምን የጸጥታ ችግር ወደሚፈለገው የማድረስ ሥራ ሥለመከናወኑም አንስተዋል።
የምርጫ ቦርድ ሕግን በጠበቀ መንገድ በምርጫ ጣቢያዎች የጸጥታ ኃይሉ ስምሪት ተሰጥቶት እየተሠራ እንደኾነ ነው የገለጹት።
ዘጋቢ:- ዘመኑ ይርጋ
የአሚኮ ዲጅታል ቤተሰአሚኮ_ዜናብ ይሁኑ!
https://linktr.ee/Amharamediacorporations
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን !
