
ጎንደር፡ ግንቦት 22/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በጎንደር ከተማ ነዋሪ ከኾኑት አካል ጉዳተኞች መካከል አቶ እንዳልክ ተፈራ እና አቶ መሳፍንት ጌትነት ለአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ እንደተናገሩት ቀደም ሲል የምርጫ ካርድ ወስደው የምርጫውን ዕለት እየተጠባበቁ ይገኛሉ።
🗳️ እንደ አካል ጉዳተኛ በቀጣይ የሚያስፈልጋቸውን ልዩ ፍላጎት ለማሟላት በምርጫው በንቃት መሳተፍ ወሳኝ መኾኑን ይገልጻሉ። በዚህም የፊታችን ግንቦት 24/2018 ዓ.ም በሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ የሚበጃቸውን ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።
🗓️ ምርጫ የነገን እጣ ፈንታ ለመወሰን የሚያገለግል የዴሞክራሲ መሣሪያ በመኾኑ አካል ጉዳተኞችም የዜግነት ግዴታቸውን በምርጫ በመሳተፍ ሊያረጋግጡ እንደሚገባ ነው የገለጹት።
#አሚኮ #ምርጫ2018 #ጎንደር #ኢትዮጵያ🇪🇹
ዘጋቢ:- አሰፋ ልጥገበው
የአሚኮ ዲጅታል ቤተሰብ ይሁኑ
https://linktr.ee/Amharamediacorporations
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን !
