ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ የጎንደር ከተማን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ግንባታን ጎበኙ።

3

 

ጎንደር: ግንቦት 16/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የጎንደር ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ግንባታ በመጠናቀቅ ደረጃ ላይ ነው። ግንባታው የማጠናቀቂያ ሥራዎች እየተሠሩለት መኾኑ ተመላክቷል።

ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ግንባታው በጥራት እየተገነባ መኾኑን ገልጸዋል። በአጭር ጊዜ ተጠናቅቆ ለአገልግሎት ክፍት እንዲኾንም አሳስበዋል።

በጉብኝቱ ከርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ በተጨማሪ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል፣ የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ይርጋ ሲሳይ እና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎችም ተገኝተዋል።

ዘጋቢ:-ታርቆ ክንዴ

#አሚኮ_ዜና #መሶብ_የአንድማዕከል አገልግሎት #ጎንደር #አማራ_ክልል #ኢትዮጵያ

የአሚኮ ዲጅታል ቤተሰብ ይሁኑ

https://linktr.ee/Amharamediacorporations

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን !

Previous article“ምርጫው ሰላማዊ እና ፍትሐዊ እንዲኾን የድርሻችንን እንወጣለን” የአልብኮ ወረዳ ነዋሪዎች
Next articleበደሴ ዙሪያ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ ዕጩዎች ትውውቅና የምርጫ ቅስቀሳ ተካሄደ።