
ባሕር ዳር፡ ግንቦት 09/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባጋሩት መልእክት “የኢትዮጵያ መልክ፤ የፍቅር ርዕስ፣ የሥልጣኔ እና የዘመናዊነት ተምሳሌት ወደሆነችው ድሬዳዋ ገብተናል” ብለዋል።
የምድር ባቡር ፈርጥ፣ የንግድና የኢንዱስትሪ ማዕከል በሆነችው ድሬዳዋ ሲደርሱ ደማቅ አቀባበል ላደረጉላቸው ለከተማዋ ከፍተኛ አመራሮች፣ ለሀገር ሽማግሌዎች እና ለከተማው ሕዝብ ምስጋና አቀርበዋል።
በድሬዳዋ ቆይታቸውም በከተማዋ እየተሠሩ የሚገኙ ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው እንደሚመለከቱ ገልጸዋል።
#አሚኮ #visit #ድሬዳዋ #ኢትዮጵያ
የአሚኮ ዲጅታል ቤተሰብ ይሁኑ
https://linktr.ee/Amharamediacorporations
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
