በአማራ ክልል ስኬታማ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችል የፓለቲካ ምሕዳር ተፈጥሯል።

2
🤝⚖️🗳️​ባሕር ዳር፡ ግንቦት 07/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በአማራ ክልል ስኬታማ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችል የፖለቲካ ምሕዳር መኖሩ ተገልጿል።
በአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ባሕል ግንባታ ዘርፍ ኀላፊ መስፍን አበጀ (ዶ.ር) በምርጫው ለመሳተፍ የሚያስችል ሰፊ የፖለቲካ ምሕዳር መኖሩን ተናግረዋል።
በዚህም ከበፊቱ በተሻለ መንገድ ፓርቲዎች ፕሮግራሞቻቸውን እና አማራጭ ሀሳቦቻቸውን በተለያዩ አማራጮች ሲያስተዋውቁ መቆየታቸውንና እያስተዋወቁ መሆኑን አብራርተዋል።
🗣️ 📢 የምርጫ ቅስቀሳዎች እና የክርክር መድረኮችም በነጻነት ሲከናወኑ መቆየታቸውን ጠቁመዋል። በሂደቱም ብልጽግናን ጨምሮ በርካታ ፓርቲዎች በንቃት መሳተፋቸውን ተናግረዋል።
የሚያጋጥሙ ችግሮችንም በየጊዜው እየተገናኙ በመፍታት ለምርጫው ዝግጅት ለማድረግ አስቻይ ሁኔታዎች እንደተፈጠሩም ነው የተናገሩት።
በሂደቱም በክልሉ የፖለቲካ ምሕዳሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን የሚያመላክት ስለመኾኑም ተናግረዋል።
የአሚኮ ዲጅታል ቤተሰብ ይሁኑ
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous article“ለሀገር ሰላም እና ለዴሞክራሲያዊ ምርጫ ስኬት በጋራ እንቁም” አቶ ተስፋሁን ዓለምነህ
Next articleምርጫ ዜጎች መብታቸውን እንዲለማመዱ ከማገዙም ባለፈ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ መሠረት ነው።