ቭላድሚር ፑቲን የዩክሬን ጦርነት ወደ ማብቂያው እየተቃረበ ነው አሉ።

4

 

ባሕር ዳር: ግንቦት 02/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የዩክሬን ጦርነት ሊያበቃ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥተዋል።

ፕሬዝዳንቱ ዘላቂ የሰላም ስምምነት ከተረቀቀ በሦሥተኛው ሀገር ከቮሎዲሚር ዘለንስኪ ጋር ለመገናኘት ፈቃደኛ መኾናቸውን አልጀዚራ አረጋግጧል። ይህ አስተያየት የተሰጠው ሩሲያና ዩክሬን ለሦሥት ቀናት የተኩስ አቁም ለማድረግ እና ሺህ እስረኞችን ለመለዋወጥ ከተስማሙ በኋላ ነው።

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሁለቱ ሀገራት የተኩስ አቁም ጥያቄያቸውን በመቀበላቸው የሰላም ድርድሩ መቃረቡን ገልጸዋል።

ፑቲን ከዘለንስኪ ጋር የሚኖረው ግንኙነት ለድርድር ሳይኾን የተጠናቀቀን ስምምነት ለማፅደቅ ብቻ መኾን እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል።

ለዓመታት የዘለቀው ይህ ጦርነት በሩሲያ ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጫና አሳድሯል። ሞስኮ አሁንም ከዩክሬን ግዛት ሲሶ ያነሰውን ክፍል ከመቆጣጠር ያለፈ ድል አላሳካችም።

ፑቲን ከአውሮፓ ጋር ስለ ወደፊቱ የጸጥታ ሁኔታ ለመወያየት ያላቸውን ፍላጎት ቢገልጹም ለንግግር የሚመርጡት ግን የቀድሞውን የጀርመን ቻንስለር ጌርሃርድ ሽሮደርን መኾኑን ጠቁመዋል።

ዘጋቢ:- ስማቸው አጥናፍ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ባለፉት ዓመታት ከተፈጠሩ የሥራ ዕድሎች ውስጥ 51 በመቶው ሴቶችን ተጠቃሚ ያደረጉ ናቸው” ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Next articleየአማራ ክልል ሚሊሻ ኮሚሽን የ30ኛ ዓመት የሚሊሻ ምስረታ በዓልን በቡልጋ ከተማ እያከበረ ነው።