ኢራን የኒውክሌር ድርድሩ በማዕቀቦች መነሳት ላይ ይመሠረታል አለች።

4

 

ባሕር ዳር፡ ግንቦት 01/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ኢራን ከአሜሪካ የቀረበላትን የሰላም ጥያቄ እየመረመረች መኾኑ ተገልጿል። ምላሽ ለመስጠትም እስካሁን ምንም ዓይነት የጊዜ ገደብ እንዳላስቀመጠች ማስታወቋን አልጀዚራ ዘግቧል።

ቴህራን ሂደቱ በደረጃ እንዲከናወን ፍላጎት እንዳላትም አስታውቃለች። ስለ ኒውክሌር መርሐ ግብሯ ድርድር ከመጀመሩ በፊት ቀጣናዊ ግጭቶች እንዲቆሙ እና የተጣሉባት የኢኮኖሚ ማዕቀቦች እንዲነሱ ቅድመ ሁኔታም አቅርባለች።

በሆርሙዝ የባሕር ሰርጥ የጸጥታ ሁኔታ እና በዩራኒየም የማበልጸግ ሂደት ላይ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው አለመግባባት አሁንም እንደቀጠለ ይገኛል።

ዘጋቢ፦ስማቸው አጥናፍ

የአሚኮ ዲጅታል ቤተሰብ ይሁኑ

https://linktr.ee/Amharamediacorporations

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን !

Previous articleጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ( ዶ.ር) በጅቡቲው ፕሬዝዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌን የበዓለ ሲመት ላይ ተገኝተዋል።
Next articleደረጃውን የጠበቀ የዓሣ ማስገሪያ በመጠቀም የዓሣ ሀብት ልማትን ለማሳደግ እየተሠራ ነው።