
ባሕር ዳር፡ ሚያዚያ 30/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በደብረ ብርሃን ከተማ አሥተዳደር ሥር በሚገኙ 5 ክፍለ ከተሞች የሚኖሩ ነዋሪዎች፣ በመጪው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ በንቃት እንደሚሳተፉ በአደባባይ ሰልፍ ገለልጸዋል።
ነዋሪዎቹ በሰልፉ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ምርጫ የሥልጡንነት መገለጫ ከመሆኑም ባለፈ ለዴሞክራሲ ግንባታና ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥ መሠረት መኾኑን አንስተዋል።
ሂደቱ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ ፍትሐዊ፣ ሚዛናዊ እና ነጻ ሆኖ እንዲከናወን አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውንም አረጋግጠዋል።
ሰልፉ የከተማዋ ነዋሪዎች ለሀገራዊ የምርጫ ሂደት ያላቸውን ከፍተኛ ተነሳሽነት ያሳየ እንደነበር ተገልጿል።
የአሚኮ ዲጅታል ቤተሰብ ይሁኑ
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን !
See less
