በጎንጅ ቆለላ ወረዳ የመራጮች ምዝገባ በንቃት እየተካሄደ ነው።

6
ባሕር ዳር፡ ሚያዚያ 07/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በሰሜን ጎጃም ዞን በጎንጅ ቆለላ ወረዳ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች እየተከናወነ ይገኛል።
‎​ምዝገባው ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ በርካታ የወረዳው ነዋሪዎች የዜግነት ኀላፊነታቸውን ለመወጣት ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በመውጣት ካርድ በመውሰድ ላይ ናቸው። ሂደቱ በቴክኒክና በቁሳቁስ ዝግጅት የታገዘ በመሆኑ ምዝገባው ያለምንም መስተጓጎል እየተካሄደ መኾኑ ተመላክቷል።
‎እድሜያቸው 18 ዓመትና ከዚያ በላይ የኾኑ፣ እንዲሁም በወረዳው ውስጥ በቋሚነት የሚኖሩ ዜጎች ሕጋዊ መታወቂያቸውን በማቅረብ እየተመዘገቡ መኾኑን የኸረዳው የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን መረጃ ጠቁሟል።
‎​
‎​ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ መሰረት ነው። ድምጽ መስጠት ደግሞ መብት ብቻ ሳይሆን ለሀገር የሚበረከት የዜግነት ኀላፊነት ጭምር ነው።
‎በምርጫዬ የሞባይል መተግበሪያ ራስዎን ለመራጭነት ይመዝግቡ!
● ከአፕ-ስቶር:- https://url-shortener.me/IHPC
● ከፕለይ-ስቶር https://url-shortener.me/IHPF ላይ በማውረድ ወይም
●በድረ-ገጽ አማራጭ (በቀጥታ) https://url-shortener.me/IHPH ይመዝገቡ።
የዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ተግባራዊ የሚደረግባቸውን ምርጫ ጣቢያዎች በአስተያየት መስጫ ሣጥን ውስጥ ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ያገኛሉ። በቀሪ ምርጫ ጣቢያዎች የማንዋል የምዝገባ ሥርዓት ተግባራዊ ይሆናል።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous articleመረጃን ከመቀበል በፊት ለምን? በማን? እንዴት’ን? ማስቀደም!
Next articleምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመሥገን ጥሩነህ ለሥራ ጉብኝት ኮምቦልቻ ገብተዋል።