ፈተናዎች ያበረቷት ተማሪ ሶሊያና ማሩ

6


‎በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ከተፈተኑት አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች መካከል ከፍተኛ ውጤት ያመጣች የባሕር ዳር ከተማ እንቁ አግኝተናል።

‎የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዋ ሶሊያና ማሩ ከ600 ውስጥ 437 በማምጣት ስኬት አስመዝግባለች፡፡ በመጣውም ውጤት በእጅጉ መደሰቷን ገልጻለች።

‎ለውጤቱ መሳካት የቤተሰቦቿ ያልተቆጠበ ድጋፍ፣ የትምህርት ቁሳቁስ አቅርቦት እና የመምህራን ልዩ ድጋፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል ብላለች።

‎”አካል ጉዳተኝነት ፈጣሪ የሰጠኝ ጸጋ ነው” ያለችው ተማሪ ሶሊያና አልችልም ብሎ ተስፋ መቁረጥ አያስፈልግም፤ የሚመጡ ፈተናዎች በሙሉ መሸጋገሪያዎች ናቸው በማለት ለሌሎች ተማሪዎች እና ጓደኞቿ ጥንካሬ የሚኾን መልእዕት አስተላልፋለች።

‎የዩኒቨርሲቲ ትምህርቷን በሕግ ትምህርት ለመቀጠል ፍላጎት እንዳላትም ተናግራለች፡፡ ወደ ትምህርት ቤት በምትመላለስበት ጊዜ የሚገጥማትን የእግር መንገድ ድካም ለማቃለል በኤሌክትሪክ (በዘመናዊ ሞተር) የሚሠራ ዊልቼሮች ድጋፍ እንዲደረግላትም ጥሪዋን አቅርባለች።

‎#ባሕር_ዳር #መስከረም_08_2019_ዓ_ም

ዘጋቢ፡- ፍሬሕይወት አዘዘው

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

Previous articleበምርት ዘመኑ በአማራ ክልል በግብርናው ዘርፍ ምን ለማሳካት ታቅዷል?
Next articleከግብርና ማዘመን እስከ ዘላቂ ሰላም