
በብሔረሰብ አሥተዳደሩ ባንጃ ወረዳ አስኩና አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በተካሄደው የማስጀመሪያ መርሐ ግብር የብሔረሰብ አሥተዳደሩ እና የባንጃ ወረዳ የሥራ ኀላፊዎች ተገኝተዋል። የባንጃ ወረዳ ዋና አሥተዳዳሪ ፀሐይነህ ቦጋለ የትምህርት ዘመኑን በስኬት ለማጠናቀቅ የተማሪ፣ የወላጆች እና የትምህርት ቤቶች ትስስር መጠናከር እንደሚገባው አስገንዝበዋል።
ተማሪዎች የወደፊት ሕይወታቸው የተቃና እንዲኾን በርትተው መማር እንደሚገባቸውም አሳስበዋል። የብሔረሰብ አሥተዳደሩ ትምህርት መምሪያ ኀላፊ ደስታው ዓለሙ የትምህርት ዘመኑ የመጀመሪያው ቀን የመማር ማስተማር ሥራ አስፈላጊ የኾኑ ቅድመ ዝግጅቶች ተጠናቀው መጀመሩንም ተናግረዋል።
ወላጆች ልጆቻቸውን በወቅቱ ወደ ትምህርት ቤት በመላክ የሚፈጠረውን የትምህርት ጊዜ ብክነት ማስቀረት እንደሚገባቸው አሳስበዋል።
በብሔረሰብ አሥተዳደሩ በትምህርት ዘመኑ ከ476 ሺህ በላይ ተማሪዎች በትምህርት ገበታ ይገኛሉ ተብሎም ይጠበቃል።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
