ጠላት ጋር አንሠራም፤ የሕዝብን ስቃይም አናራዝምም

14
🚨
በሰሜን ጎንደር ዞን በጫካ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች ግጭቱ የሀገርን ኢኮኖሚ የሚጎዳ፤ የሕዝብን ሰቆቃ የሚያራዝም መኾኑን በመረዳት የሰላም አማራጭን መቀበላቸውን ተናግረዋል።
የትጥቅ ትግሉ ከታሪካዊ ጠላቶች ጋር ጥምረት በመፍጠር የግለሰቦችን ጥቅም ለማስከበር የሚደረግ፤ በታጣቂዎች መካከል የእርስ በእርስ ግጭት የጎላበት እና ዓላማ የሌለው መኾኑንም አንስተዋል።
በቀጣይ ሰላምን ለማጽናት እና በጫካ የሚገኙ ታጣቂዎች የሰላምን አማራጭ እንዲቀበሉ የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡ ገልጸዋል።
የሰሜን ጎንደር ዞን ሰላም እና ጸጥታ መምሪያ ኀላፊ ዳኝነት ሙሉሰው የሰላም አማራጭ የተቀበሉ ታጣቂዎችን መልሶ ለማቋቋም እየተሠራ መኾኑን ተናግረዋል።
የሰሜን ጎንደር ዞን አሥተዳዳሪ ዲያቆን ሸጋው ውቤ በዞኑ በርካታ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን በመቀበል በቡድን እየገቡ ነው ብለዋል። ተደጋጋሚ ውይይት በማድረግ እስከ ትጥቃቸው የሰላም አማራጭን እንዲቀበሉ ተደርጓል ነው ያሉት።
✅ሰላምን ለማጽናት የዞኑ ተሞክሮ
👉 ታጣቂዎች እስከ ትጥቃቸው የሰላም አማራጭን እንዲቀበሉ ተደርጓል።
👉 የሃይማኖት አባቶች፤ የሀገር ሽማግሌዎች እና ማኅበረሰቡ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭ እንዲቀበሉ በቁርጠኝነት ሠርቷል ነው ያሉት።
👉የሰላምን አማራጭ የተቀበሉ ታጣቂዎችን በጸጥታ መዋቅሩ ውስጥ በማስገባት ሰላምን እንዲያጸኑም እየተሠራ ነው ብለዋል።
✅ታጣቂዎች የሰላም አማራጭ መቀበላቸው ምን ውጤት አመጣ ?
👉ታጣቂዎች በነበሩበት አካባቢ የተቋረጡ የመንግሥት አገልግሎቶች ክፍት እንዲኾኑ አስችሏል ነው ያሉት።
👉የልማት ሥራዎችን ለማሥጀመር ዕድል ፈጥሯል፤ ግድያ፤ ዘረፋ እና እገታዎች እንዲቆሙም አድርጓል ብለዋል። ትምህርት ቤቶች ተማሪዎችን እንዲመዘግቡ፣ ማኅበረሰቡ በነጻነት እንዲንቀሳቀስ ዕድል መፍጠሩንም ተናግረዋል።
ዞኑ በሰሜኑ ጦርነት የተጎዳ መኾኑን ያነሱት አሥተዳዳሪው ታጣቂዎች ከታሪካዊ ጠላት ጋር አንሠራም፤ የሕዝብን ስቃይ አናራዝምም በማለት የሰላም አማራጭን መቀበላቸውን ገልጸዋል።
የሰላምን አማራጭ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎች በጫካ የሚገኙ ታጣቂ ኀይሎች የሰላምን አማራጭ እንዲቀበሉ የበኩላቸውን ጥረት እያደረጉ መኾኑንም ገልጸዋል።
የሰላም አማራጭን በማይቀበሉ ታጣቂዎች ላይ ሕግ የማስከበር ተግባሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል።
ዘጋቢ:- ያየህ ፈንቴ
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
Previous article“ለሰላም እጦት መድኃኒቱ ቅን አዕምሮ ነው”
Next article18ተኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ለኢትዮጵያ ያለውን ድጋፍ ያሳየባቸው ጉዳዮች ምንድን ናቸው ?