‎በበጀት ዓመቱ ግልፅ፣ ተጨባጭ እና አካባቢያዊ ፀጋዎችን መሠረት ያደረገ እቅድ ይተገበራል።

2
‎‎”አርቆ ማየት፣ አልቆ መሥራት” በሚል መልዕክት በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር የ2018 በጀት ዓመት የፓርቲ እና የመንግሥት ሥራዎች
አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ውይይት መድረክ መካሄድ መካሄድ ጀምሯል። ‎በመድረኩም የብሔረሰብ አስተዳደሩ፣ የወረዳዎች እና ከተማ አስተዳደር ጠቅላላ አመራሮች እየተሣተፉ ነው።
‎ባለፈው በጀት ዓመት ተደራራቢ ችግሮችን ተቋቁመን ስኬቶችን አስመዝግበናል ያሉት የብሔረሰብ አስተዳደሩ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ዳግም ባይነሳኝ ናቸው።
‎አመራሩ ቅንጅታዊ አሠራርን ይበልጥ ማሣደግ የሚያሥችሉ አሠራሮችን ተግባራዊ ማድረግ ማሥቻላችን የስኬቶች መመዝገብ ቀዳሚ ምክንያቶች እንደሆኑም አክለዋል።
‎በበጀት ዓመቱ የተገኙ ስኬቶችን ተሞክሮ በመቀመር የማሥፋት ሥራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የጠቆሙት ኃላፊው በበጀት ዓመቱ ግልፅ፣ ተጨባጭና አካባቢያዊ ፀጋዎችን መሠረት ያደረገ እቅድ በማቀድ ለውጤታማነቱ ቅንጅታዊ አሠራርን ማጠናከር እንደሚገባ ጠቁመዋል።
‎የባለፈው በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በብሔረሰብ አስተዳደሩ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አበባ ወርቁ እየቀረበ ነው።
‎የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
Previous articleከሰላም እስከ ልማት – የባሕር ዳር ከተማ ጉዞ !
Next article‎የምዕራብ ጎንደር ዞን “አርቆ ማየት፣ አልቆ መሥራት” በሚል መሪ ሀሳብ ግምገማና ውይይት እያካሄደ ነው።