‎በተያዘዉ በጀት ዓመት የዞኑን ማኅበረሰብ ቀጥተኛ ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ሥራዎች ላይ ትኩረት ይደረጋል።

4
‎በሰሜን ሸዋ ዞን የ2018 በጀት ዓመት የፓርቲና የመንግስት ሥራዎች ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ መድረክ በደብረብርሃን ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
‎​በመድረኩ ላይ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ መካሻ ዓለማየሁ ዞኑ በ2018 በጀት አመት የሥራ አፈጻጸም በክልል ደረጃ የሁለተኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁ የአመራሩ ቁርጠኝነትና የመናበብ ውጤት መሆኑን ተናግረዋል።
‎የተገኘው ውጤት በ2019 በጀት ዓመት በሕዝብና በመንግሥት የተያዙ ዕቅዶችን ለማሳካት ትልቅ ስንቅ እንደሚሆን ገልጸዋል።
‎​በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት የተመዘገቡ መልካም ውጤቶችን እንደ መነሻ በመጠቀም በተያዘዉ በጀት ዓመት የዞኑን ማኅበረሰብ ቀጥተኛ ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ሥራዎች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሠራ አረጋግጠዋል።
‎ሕዝቡን የሚመጥን የተሟላ ሰላምና ልማት ለማረጋገጥ አመራሩ በቁርጠኝነት ሊሠራ እንደሚገባም አሳስበዋል።
‎​በውይይት መድረኩ ላይ የሰሜን ሸዋ ዞንየ2018 በጀት አመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ ጥልቅ ግምገማ እየተደረገ ይገኛል።
‎በመድረኩ ላይ በዞኑ የሚገኙ የወረዳና ከተማ አስተዳደር አመራሮች ተገኝተዋል።
‎ዘጋቢ፦ዮናስ ታደሰ
‎የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
Previous articleየ2019 ዓ.ም የሬሜዲያል መርሐ ግብር የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥብ ይፋ ሆነ።
Next articleየሕዝቡን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ሰፊ ጥረት ተደርጓል።