‎”ስኬቶቻችንን የሞራል ስንቅ አድርገን በአዲሱ ዓመት የላቀ ውጤት ለማምጣት በቁጭት እንተጋለን” ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ

11

‎”ስኬቶቻችንን የሞራል ስንቅ አድርገን በአዲሱ ዓመት የላቀ ውጤት ለማምጣት በቁጭት እንተጋለን” ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ

‎የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ለ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል፦

‎እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ!!

‎አዲስ ዓመት የበለጠ ተስፋ የምንሰንቅንበት፣ ቂምና ጥላቻን በይቅርታ ሽረን በአብሮነት የምንሻገርበት ጊዜ ይሁንልን።

‎አዲሱ ዓመት ለመጪው ትውልድ አሻራ የምናስቀምጥበት፤ ያለንን ዕምቅ የመልማት ፀጋ ከሕዝባችን አቅም ጋር አቀናጅተን በመጠቀም ልማታችን የምናፋጥንበት ዓመት ይሆናል።

‎ዘላቂ ሰላማችንን አፅንተን፤ አብሮነታችንና ትብብራችንን ካጠናከርን ከፊት ለፊታችን አዲስ ድልና ስኬት ይጠብቀናል። ለዚህም ቃላችን ጠብቀን የተሻለ ዘመን ለመፍጠር አልቀን እንሠራለን።

‎ስለሆነም ያጋጠሙንን ሳንካዎች ተሻግረን፤ ጉድለቶቻችንን አርመን፤ ስኬቶቻችንን የሞራል ስንቅ አድርገን በ2019 ዓ.ም የላቀ ውጤት ለማምጣት በቁጭት እንተጋለን።

‎አዲሱ ዓመት ሁሉም ኢትዮጵያውያን ትብብራችን እና አብሮነታችን የበለጠ የሚጠናከርበት፤ የእድገትና የብልፅግና ዘመን እንዲሆንልን እመኛለሁ።

‎ መልካም አዲስ ዓመት!


‎#ባሕር_ዳር #ጳጉሜን_05_2018_ዓ_ም

‎የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

Previous article“በይቅርታ ሂደት የተፈቱ ወገኖች በሀገራዊ ምክክር ምክረ ሐሳቦች ላይ አዎንታዊ ሚና ይጫወታሉ ተብሎ ይታመናል” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር)
Next article‎”ለሰላም እና ለዕድገት ዋነኛ መፍትሄ የኾነውን አብሮነትን ባሕል ልናደርግ ይገባል”