“የኢትዮጵያን ትንሣኤ ወደ ዘላቂ ብልጽግና ከፍ እናደርጋለን” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር)

12

 

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) የማንሠራራት ቀንን አስመልክተው መልእክት አስተላልፈዋል። የመልእክታቸው ሙሉ ይዘት እንደሚአተለው ቀርቧል፦

ከቃል ባለፈ በተጨባጭ ስኬት የቆመችው ኢትዮጵያ!

ትናንት “ኢትዮጵያ ተነሥታለች” ስንል ምኞት ሳይኾን ዛሬ በተጨባጭ ያረጋገጥነው እውነት ነው! ከታላቁ ሕዳሴ ግድብ ማማ እስከ ዘመናዊው የኮሪደር ልማት፣ ከቢሾፍቱ ሜጋ አውሮፕላን ማረፊያ እስከ ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ድረስ ሀገራዊ መነቃቃታችን በተግባር ተመስክሯል።

ይህ ለውጥ በዜጎቻችን የኑሮ ደረጃ፣ በከተሞች መዘመንና የሥራ ዕድል ላይ እውነተኛ ብርሃን ከመሆኑም በላይ ለልጆቻችን የነገ ብሩህ ተስፋን የሚሰንቅ ታላቅ ርዕይ ነው።

ከእንግዲህ ወደኋላ አንመለስም! በጀመርነው ታሪካዊ የማንሠራራት ጉዞ የልማት ኃይላችንን ይበልጥ በማፋጠን የኢትዮጵያን ትንሣኤ ወደ ዘላቂ ብልጽግና ከፍ እናደርጋለን።

#አሚኮ #EthiopiaDelivers #Ethiopia

Previous articleየሀገር መከላከያ ሠራዊት ሀገር የሚጠብቅ ብቻ ሳይኾን አምራች ኀይልም ነው።
Next articleየኩረጃ ባሕልን ያስቀረው የትምህርት መዋቅራዊ ለውጥ