
የአማራ ክልል ከተማ እና መሠረተ ልማት ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ፣ የ2019 ዕቅድ ትውውቅ እና በአዲሱ የከተማ ልማት ፖሊሲ ዙሪያ ውይይት አካሂዷል።
የአማራ ክልል ከተማ እና መሠረተ ልማት ቢሮ ኀላፊ ሞላ መልካሙ (ዶ.ር) በ2018 በጀት ዓመት በሪጅዮፖሊታንት እና በሌሎች ከተሞች ሰፊ የኮሪደር ልማት ሥራዎች መሠራታቸውን ተናግረዋል። ከመደበኛ መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች አኳያ 95 በመቶ የሚኾኑት
መጠናቀቃቸውንም ገልጸዋል። የአንድ ከተማ አንድ ፕሮጀክት ሥራም በ230 ከተሞች ተግባራዊ መደረጉን ጠቅሰዋል። 606 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ደግሞ በከተማ ምግብ ዋስትና ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል።
በድረኩ የተሳተፉ የከተሞች የሥራ ኀላፊዎችም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የኮሪደር እና የቤቶች ልማት፣ የተቋማት ግንባታ እና አገልግሎት አሰጣጥን ማሻሻል እንዲሁም የመንገድ መሠረተ ልማት ተግባራትን በዋናነት ትኩረት ሰጥተው መሥራታቸውን አንስተዋል።
በቀጣዩ በጀት ዓመትም የተጀመሩ ልማቶችን ማስቀጠል፣ የቤቶች ልማት፣ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን በትኩት እንደሚሠሩ ገልጸዋል።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
