“የዳኝነት እና የፍትሕ ሥርዓት ግንባታዎች ለሀገር ዕድገት የላቀ ድርሻ አላቸው” አቶ አለምዓንተ አግደው

4
የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፍርድ ቤቶችን የ2018 በጀት ዓመት እና የባለፉትን ሦሥት ዓመታት የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ አፈጻጸም እየገመገመ ነው።
🎤 በመድረኩ መልዕክት ያስተላለፉት የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ዓለምአንተ አግደው “የዳኝነት እና የፍትሕ ሥርዓት ግንባታ ለሀገር እድገት የላቀ ድርሻ አላቸው” ብለዋል፡፡
ፍርድ ቤቶች ሕግን እና ማስረጃን መሠረት በማድረግ ለዜጎች የንብረት፣ የፈጠራ፣ የሰብዓዊ መብት እና ደኅንነት መከበር ለሀገር ዕድገት መሠረታዊ የኾኑ ተቋማት መኾናቸውን ገልጸዋል።
የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤትም በሕገ መንግሥት እና በሌሎች ዝርዝር ሕጎች የተሰጠውን ኀላፊነት በአግባቡ ለመወጣት ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መኾኑን ጠቁመዋል።
🏛️ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጡን በማሻሻል፣ የሕዝብ አመኔታ የተቸረው በማድረግ በሀገር ደረጃ ተምሳሌት የኾነ ፍርድ ቤት የመገንባትን ርዕይ ይዞ እየሠራ ይገኛል ነው ያሉት፡፡
ይህንንም እውን ለማድረግ ከ2016 ዓ.ም እስከ 2018 ዓ.ም ተግባራዊ የሚደረግ የዳኝነት እና የፍትሕ ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ተዘጋጅቶ ሢሠራ መቆየቱን ገልጸዋል።📜
ከዚህም የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድን በማዘጋጀት፣ ልዩ ትኩረት የሚሻቸውን ሥራዎች በ100 ቀናት ዕቅድ ውስጥ በማካተት ሲተገብር ቆይቷል ነው ያሉት። በዚህም ተጨባጭ ለውጦች እና ውጤቶችን ማስመዝገብ እንደተቻለ አስታውቀዋል፡፡
👥ለሰው ሀብት ግንባታ ትኩረት በመስጠትም ለዳኞች፣ ለፍርድ ቤቱ መሪዎች እና ሠራተኞች የአገልጋይነት መንፈስ ለመጨመር የሚያስችሉ ተግባራት ተከናውነዋል ብለዋል፡፡ ሰፊ ሥልጠና በመስጠትም የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጡን ቀልጣፋ እና ውጤታማ ለማድረግ ጥረት መደረጉንም ገልጸዋል፡፡
🎓 በዘርፉ የልህቀት ማዕከል እንዲኾን የሚያስችል የሕግ እና ፍትሕ ኢንስቲትዩት እንደገና በማደራጀት ወደ ሥራ እንዲገባ መደረጉንም ጠቁመዋል፡፡
🏘️ በክልሉ የባሕል ፍርድ ቤቶች ተቋቁመው ሥራ እንዲጀምሩ መደረጉንም አብራርተዋል። ይህም ፍትሕን ለዜጎች ተደራሽ ከማድረግ ባለፈ ዘላቂ ሰላምን በመገንባት በኩል አስተዋጽኦ ይኖረዋል ነው ያሉት፡፡
🌍ዓለም አቀፍ የግልግል ዳኝነት ማዕከል በባሕር ዳር ከተማ ለማቋቋም የሚያስችሉ ሰፊ የዝግጅት ሥራዎች መሠራታቸውንም ተናግረዋል፡፡ ይህም በክልሉ የፍትሕ ቱሪዝምን ከማስተዋወቅ ባለፈ ለሀገር የኢኮኖሚ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው አመላክተዋል፡፡
የዳኝነት ነፃነት እና ገለልተኝነትን ከማረጋገጥ አንጻር ብዙ ተጨባጭ ሥራዎች መሠራታቸውንም ገልጸዋል፡፡፡
ለፍርድ ቤቱ ስኬት አስተዋጽኦ ላደረጉ በየደረጃው ላሉት የመንግሥት ተቋማት፣ አስፈጻሚዎች፣ ምክር ቤቶች፣ የፍትሕ ተቋማት ትብብር፣ የማስረጃ ሰጭዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ምሥጋና አቅርበዋል።🙏
#ባሕር_ዳር ሐምሌ 8/2018 ዓ.ም
✍️ዘጋቢ:- አሰፋ ልጥገበው
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
Previous articleየኢትዮጵያ የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የላቀ አገልግሎት እንዲሰጥ መሥራት ይገባል።
Next articleበማክሮ ኢኮኖሚው ላይ አዎንታዊ ለውጥ ለማምጣት እየተሠራ ነው።