
የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የመቶኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እና 5ኛውን የሕብረተሰብ ጤና ሳይንሳዊ ጉባኤ ሊያከብር ነው።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሳይ ኃይሉ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ ተቋሙ ዛሬ ላይ ለደረሰበት ታላቅ ደረጃ ለመብቃት ባለፉት 100 ዓመታት ውስጥ በርካታ ውጣ ውረዶችንና መዋቅራዊ ለውጦችን ማለፉን ገልጸዋል።
ከሩሲያ ቀይ መስቀል እስከ አሁኑ የሕክምና ማዕከል የኢንስቲትዩቱ ታሪክ የጀመረው በሩሲያ ቀይ መስቀል የጤና ባለሙያዎች አማካኝነት ዘመናዊ የላብራቶሪ አገልግሎት በመጀመር ነበር። በጥቂት ባለሙያዎች እና በአንዲት ማይክሮስኮፕ ስራውን የጀመረው ተቋሙ፣ በሂደት፦
በሀገር ውስጥ አቅም ታሪክ መስራት! ኢንስቲትዩቱ አሁን ላይ በደረሰበት ዘመናዊ የላብራቶሪ ብቃት፣ እንደ ማርበርግ እና የዝንጀሮ ፈንጣጣ (Mpox) ያሉ አስፈሪ በሽታዎችን ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ አቅም መመርመር መለየት መቻሉ ተገልጿል። በተጨማሪም፦
#ባሕር_ዳር፡ ሐምሌ 07/2018 ዓ.ም
ዘጋቢ: አየለ መስፍን
