
የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር በቴክኒክ እና ሙያ ዘርፍ የሥልጠና ጥራትን ለማረጋገጥ እየሠራ ይገኛል፡፡
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ባደረገው ኦዲት መሠረት ዕውቅና ካገኙ የፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች መካካል ደብረ ማርቆስ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጁ አንዱ ነው።
የደብረ ማርቆስ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አስጨነቅ ካሳ ኮሌጁ ላለፈው አንድ ዓመት ሲያከናውን የነበረውን ጥልቅ የውስጥ ዝግጅት እና የጥራት ማረጋገጫ ኦዲት በተሳካ ሁኔታ በማጠናቀቅ፣ የአይ ኤስ ኦ 21001:2018 የትምህርት ተቋማት አሥተዳደር ሥርዓቶች የተሰኘ ዓለም አቀፍ ዕውቅና አግኝቷል ብለዋል።
ይህ ስኬት ኮሌጁ የትምህርት አሰጣጥ ሂደቱን፣ የማሽን እና የቴክኖሎጂ አቅሙን፣ የሰነድ አያያዝ ሥርዓቱን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማሳደግ የተደረገ ጥረት ውጤት መኾኑን ነው የተናገሩት። በተደረገው ኦዲትም ተቋሙ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተቀመጡ መስፈርቶችን በማሟላቱ ዕውቅናውን አገኝቷል ነው ያሉት።
ይህ ዕውቅና ለተቋሙ፣ ለሠልጣኞች እና ለአካባቢው ማኅበረሰብ ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል ብለዋል።
ዕውቅናው ከሚያስገኛቸው ጥቅሞች መካከልም
ይህ ስኬት በሀገር አቀፍ ደረጃ የቴክኒክ እና ሙያ ሥልጠናን ጥራት ከፍ ለማድረግ ጉልህ ሚና እንደሚጫወት ይጠበቃል።
ዘጋቢ፦ሥራውድንቅ ደሳለው
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
