
#ባሕር_ዳር ሰኔ 25/2018 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሂደት አሳታፊነትን እና አካታችነትን ለማረጋገጥ ምን ምን ተግባራትን አከናወነ?
☀️ ሰፊ የኅብረተሰብ ተሳትፎ፦
ምክክሩን አሳታፊ ለማድረግ የሃይማኖት ተቋማትን፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችን እና ታዋቂ ግለሰቦችን ያካተተ ነበር።
☀️ ሁለንተናዊ ተደራሽነት፦
በሁሉም ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች በመንቀሳቀስ አጀንዳዎችን የመሰብሰብ እና ወካይ ተሳታፊዎችን የመለየት ሥራ ተሰርቷል።
☀️ የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ተካፋይነት፦
ሀገር ሽማግሌዎች፣ አካል ጉዳተኞች፣ ምሁራን፣ ሴቶች፣ ወጣቶች፣ ሠራተኞች እና ተፈናቃዮች በእኩልነት እንዲሳተፉ ተደርጓል።
☀️ የዳያስፖራ ተሳትፎ፦
የምክክር ሂደቱ በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይወሰን፣ በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያንንም ያሳተፈ ነው።
☀️ ታሪካዊ የውይይት መድረክ፦
አርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ከሊቃውንትና ከመሪዎች ጋር በአንድ መድረክ ተቀምጠው ስለ ሀገራቸው የሚወያዩበት ዕድል ተፈጥሯል።
☀️ የአጀንዳዎች ምንጭ፦
የኮሚሽኑ ስምንቱ ዋና ዋና ሀገራዊ አጀንዳዎች በቀጥታ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ፍላጎት፣ ስጋት እና ተስፋ የተቀዱ ናቸው።
☀️ ለወደፊት የተቀመጠ ግብ፦
ኮሚሽኑ አሁን ካለው ዝግጅት በኋላ፣ በሰፊው ለመምከር ሐምሌ 08/2018 ዓ.ም ቀጠሮ በመያዝ ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ ተሸጋግሯል።
#አሚኮ #የኢትዮጵያ_ሀገራዊ_ምክክር_ኮሚሽን #ኢትዮጵያ_እየመከረች_ነው
