
ባሕር ዳር: ሰኔ 09/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ እና የተፋሰስ ልማትን በተመለከተ ለምዕራብ አማራ ለዞን እና ለወረዳ የተፈጥሮ ሀብት ልማት እና ጥበቃ ቡድን መሪ እና ባለሙያዎች ሥልጠና እየሰጠ ነው።
የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኀላፊ መሰሉ ብርሃኑ ሥልጠናው በ2018 በጀት ዓመት የተሠሩ የተፈጥሮ ሀብት ልማቶችን በመገምገም የቀጣይ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር አፈጻጸምን ለማሻሻል ያለመ መኾኑን ተናግረዋል።
የተፋሰስ ልማትን አርሶ አደሮች በባለቤትነት እየጠበቁ እና እየተንከባከቡ ይገኛሉም። አርሶ አደሮች
በፍራፍሬ ልማት ተጠቃሚ መኾናቸውንም ተናግረዋል።
በ2017 ከተተከሉ ችግኞች ውስጥ 80 ነጥብ 1 በመቶ መጽደቁንም ምክትል ቢሮ ኀላፊዋ ተናግረዋል።
በክልሉ በሰባት ዓመት ውስጥ 10 ነጥብ 4 ቢሊዮን ችግኝ መተከሉን ገልጸዋል። በዚህም 14 ነጥብ 6 በመቶ የነበረውን የደን ሽፋን ወደ 18 ነጥብ 9 በመቶ ማድረስ ተችሏል ብለዋል።
ይህም አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ አድርጓል ነው ያሉት። አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የደን እና ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ያላቸው ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት መደረጉንም አንስተዋል።
የውይይቱ ተሳታፊ የዘርፉ ባለሙያዎች ከአርሶ አደሮች ጋር በቅንጅት መሥራታቸውን ተናግረዋል። የችግኝ መትከያ ጉድጓዶች ቀድመው ማዘጋጀታቸውንም አንስተዋል።
ሥልጠናው አቅምን የሚያሳድግ እና ውጤታማነትን ከፍ የሚያደርግ ነው ብለዋል።
ዘጋቢ:-ያየህ ፈንቴ
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
